ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ2015 በጀት ዓመት ባለፉት 9 ወራት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡ ተገለጸ፡፡ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ግንቦት 2 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ

በስድስት ዘርፎች የተዋቀረውና በሥሩ 44 ድርጅቶችን የያዘው ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የበጀት ዓመቱን የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ገምግሟል፡፡

ምንም እንኳን በተለያዩ የድርጅቶቻችን አካባቢዎች በርካታ ተጽዕኖዎች ቢኖሩም ይህን ተቋቁሞ የሚሰራ አመራርና ሰራተኛ በመፈጠሩ ተቋሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ አመርቂ ውጤት እያመጣ መሆኑን የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አህመድ ገልጸዋል፡፡

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ኮርፖሬት ኮሙኒኬሽንና ማህበራዊ ኃላፊነት ዳይሬክተር አምባሳደር አሊ ሱለይማን በበኩላቸው ተቋሙ ከሚሰራው የኢንቨስትመንት ሥራ በተጓዳኝ በሀገሪቱ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ፈጥኖ በመድረስ አወንታዊ ምላሾችን በሚገባ የተወጣበት በጀት ዓመት እንደነበርም ተናግረዋል፡፡

በተለይም የሚድሮክ ድርጅቶች ባሉባቸው አካባቢዎች ሁሉ ማህበረሰብ ጋር ተቀራርቦ መስራት የተቋሙ ዋነኛ መገለጫ መሆኑንም አምባሳደር አሊ አስረድተዋል፡፡

በሌላ በኩል ድርጅቶቹ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮችም በበጀት ዓመቱ እንደፈተኗቸው ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

ለአብነትም ሀያ በመቶ የቡና ምርት ከእየ እርሻዎቹ ማሳ በተደራጁ ኃይሎች ቢዘረፍም፤ በላይኛው አዋሽ አግሮ ኢንደስትሪ የፍራፍሬ ምርቶች ላይ መጠነ ሰፊ ዝርፊያና ሥርቆት ቢከናወንም ድርጅቱ ይህን ተቋቁሞ ከማትረፍ እንዳላገደው ግን አመልክተዋል፡፡

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ባለፉት 9 ወራት ከአጠቃላይ የምርት ሽያጭ ከ26 ቢሊየን ብር በላይ ማግኘቱም በውይይቱ ላይ ተጠቁሟል፡፡

ABOUT MIDROC INVESTMENT GROUP
MIDROC Investment Group is a group of Sheikh Mohammed Hussien Ali Al-Amoudi’s companies, mainly engaged in Agriculture, agro-processing, Manufacturing, Mining, Construction, Real-estate, Hotel, Tourism and Commercial endeavors.

READ MORE

OUR LEADERSHIP
Our senior executives bring tremendous experience, visionary thinking and a shared commitment to excellence, creativity, and innovation to the future as well as  the day to day operation of the company.

READ MORE