ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከልዩ ሽልማት በተጨማሪም በበጎ ተግባሩ የፕላቲነየም ተሸላሚ ነው።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ2017 ዓ.ም ላከናወናቸው ሰው ተኮር ስራዎች ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልዩ እውቅናና ሽልማት ተበርክቶለታል።
የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አህመድ ሽልማቱን ተቀብለዋል።

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ ደሀ ተኮር ስራዎችን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር አከናውኗል።
የበጎነት መኖሪያ ህንፃዎች ግንባታ፣ የምገባ ማዕካላት ግንባታና ቀጣይነት ያለው የምገባ አገልግሎት፣ ዘመናዊ የእንጀራ መጋገሪያ ፋብሪካ ግንባታ፣ ፅዱ ኢትዮጵያ፣ የኩላሊት ዲያሊስስ ማሽንና ግብዓት ልገሳ፣ እንዲሁም የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም እና የወንዝ ዳር ልማትን በአብነት ማንሳት ይቻላል።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከአመታዊ ትርፉ 10 በመቶውን ማህበራዊ ሃላፊነትን ለመወጣት በመመደብ ግንባር ቀደም ተቋም ነው።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ2017 በጀት አመት 22 ድርጅቶቹ በታማኝ ግብር ከፋይነት እውቅና አግኝተዋል።
መስጠት አያጎድልም! ሚድሮክ ለሀገር— ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ









