ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከማሪዮት ኢንተርናሽናል ጋር የፍራንቻይዝ የፊርማ ስነ-ስርዓት አካሄደ::

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በስድስት ዘርፎች ተዋቅሮ በሃገራችን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ላይ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያደረገ ያለ ተቋም እንደሆነ ይታወቃል።
ከእነዚህ ስድስት ዘርፎች አንዱ አካል የሆነው የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ መሐመዲያ ቪሌጅ እና በጅማ ከተማ ለሚያስገነባቸው ሁለት ሆቴሎች ከማሪዮት ኢንተርናሽናል ጋር በፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ብራንድ የፍራንቻይዝ የፊርማ ስነ-ስርዓት አካሂዷል።
በሚድሮክ ኢንቨስትመንት በኩል ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ጀማል አህመድ እንዲሁም በማሪዮት ኢንተርናሽናል በኩል ሚስተር ካሪም ቸልቶት ፊርማቸውን አኑረዋል።
በአዲስ አበባ መሐመዲያ ቪሌጅ ላይ የሚገነባው ሆቴል፦


– የግንባታ ወጪው 2.3 ቢሊየን ብር የሚገመት ሲሆን
– ባለ 11 ወለል ህንፃ
– 250 መኝታ ክፍሎች
– የተለያዩ ስፔሻሊቲ ሬስቶራንቶች
– መዋኛ ገንዳ፣ ስፓ እና ሌሎች የመዝናኛ ፋሲሊቲዎች
የሚኖረው ይሆናል።
በጅማ ከተማ የሚገነባው ሆቴል፦
በከተማው መግቢያ ላይ በዳ ቡና በተባለውና መስህብ ባለው የተፈጥሮ ስፍራ ላይ ሲገነባ
– የግንባታ ወጪው 1.4 ቢሊየን ብር የሚገመት ሲሆን
– 5 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ
– የጅማን ባህልና ወግ በሚያንፀባርቅ መልኩ
የሚገነባ
– 120 የመኝታ ክፍሎች
– በአይነቱ ልዩ የሆነ ሰው ሰራሽ ሐይቅ
– የተለያዩ ዘመናዊ ሬስቶራንቶች
– የግራውንድ ቴኒስ መጫወቻ
– የመዋኛ ገንዳ እና ስፓ የሚያካትት ሆኖ ይገነባል።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከዚህ ቀደምም በባህርዳር እና ሐዋሳ ከተማ ላይ ለሚያስገነባቸው ሆቴሎችም ከማሪዮት ኢንተርናሽናል ጋር የፍራንቻይዝ ፊርማ መፈራረሙ ይታወሳል።

Recent News

Archives

ABOUT MIDROC INVESTMENT GROUP

MIDROC Investment Group is a group of Sheikh Mohammed Hussien Ali Al-Amoudi’s companies, mainly engaged in Agriculture, agro-processing, Manufacturing, Mining, Construction, Real-estate, Hotel, Tourism and Commercial endeavors.

READ MORE

OUR LEADERSHIP

Our senior executives bring tremendous experience, visionary thinking and a shared commitment to excellence, creativity, and innovation to the future as well as  the day to day operation of the company.

READ MORE