መስጠት አያጎድልም -ሚድሮክ ለሀገር-ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ
በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የተገነባው የሱልጣን አሊሚራህ ሃንፍሬ መስጂድ ተመረቀ።
ግንባታዉ ተጀምሮ ለ30 አመታት ተቋርጦ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ባማረ መልኩ ተጠናቆ አገልግሎት መሰጠት ጀምሯል።
መስጅዱ በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አዉሲ-ሪሱ መስተዳድር አይሳኢታ ከተማ ይገኛል።
የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ሃጂ አወል አርባ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የኢትዮጵያ እድገት ለማረጋገጥ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከመስጂድ ግንባታው በተጨማሪ በክልሉ በርካታ የኢንቨስትመንት ስራዎች ላይ በመሳተፍ ሰፊ የስራ እድሎችን እየፈጠረ መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ ሀጂ አወል አርባ ተናግረዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ባለቤትና ሊቀ-መንበር ሼይኽ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲና የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አሕመድን አመስግነዋል።
የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ በበኩላቸው ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የተለያዩ ሰዉ ተኮር ስራዎች ላይ በመሳተፍ የዜጎቻችን ኑሮ ለማሻሻል እየሰራ ነዉ ብለዋል።
ሚድሮክ ኢንቨሰትመንት ግሩፕ የሱልጣን ዓሊሚራህ ሃንፍሬን ቤተመንግሥት ገንብቶ እንደሚያስረክብም ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ ጀማል አህመድ ተናግረዋል።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከትርፉ 10 በመቶውን ለተለያዩ ማህበራዊ ኃላፊነት በመመደብ ሀገራዊ ሃላፊነቱን በመወጣት ላይ የሚገኝ የሀገር ሀብት የሆነ ተቋም ነው።
ሚድሮክ ለሀገር-ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ










