ደንቢ ኢኮ ሎጅ በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመረቀ ።

ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቤንች ሼኮ ዞን የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ ጠ/ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አሕመድ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በተገኙበት ተመርቋል።

ኢኮ ሎጁ የሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍ ባለፉት ሰባት አመታት ዘላቂነትን፣ የቅርስ ኃብትን እና ለዘመናት የሚዘልቅ አለምአቀፍ ደረጃን የመጠበቅ እድል መፍጠርን በማዋሃድ ምን ያህል እንደተለወጠ ማሳያ ነው ያሉት ጠ/ሚኒስትር ዓብይ አሕመድ (ዶ/ር) ናቸው።

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አሕመድ ሎጁ የሀገር በቀል ኢኮኖሚክ ማሻሻያው ባመጣው ዉጤት መሰረት በሀገር ዉስጥ በከፍተኛ ጥራት የተመረቱ ምርቶችን በመጠቀም ጥንካሬና ዘመናዊነትን በተላበሰ መልኩ ከአከባቢው የተፈጥሮ ሀብት ጋር እንዲስማማ ታስቦ የተሰራ ነው ብለዋል ።

በአፍሪካ ግዙፉ የቡና እርሻ በሆነው በበቃ የቡና እርሻ ልማት አጠገብ የተሰራዉ ይህ ሎጅ የክልሉን እና የሀገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ የሚያሳድግ እንደሆነ ተናግረዋል ።

ደንቢ ኢኮ ሎጅ ቱሪስቶች የማይረሳ ጊዜን እንዲያሳልፉ በከፍተኛ ጥራት በሚድሮክ ፡ኢንቨስትመንት ፡ ግሩፕ ፡ የተገነባ ነው።

ሚድሮክ የሀገር ሀብት-ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ

ABOUT MIDROC INVESTMENT GROUP

MIDROC Investment Group is a group of Sheikh Mohammed Hussien Ali Al-Amoudi’s companies, mainly engaged in Agriculture, agro-processing, Manufacturing, Mining, Construction, Real-estate, Hotel, Tourism and Commercial endeavors.

READ MORE

OUR LEADERSHIP

Our senior executives bring tremendous experience, visionary thinking and a shared commitment to excellence, creativity, and innovation to the future as well as  the day to day operation of the company.

READ MORE

  • RMOHA SOFT Drinks Industry
  • AMANUFACTURING CLUSTER QUALITY POLICY