ጥቅምት 1 ቀን 2016 ዓ.ም በሃገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የ2015 ዓ.ም የታማኝ ግብር ከፋዮች ሽልማት 18 ድርጅቶቻችን በወርቅና በብር ደረጃ ተሸላሚ ሆነዋል።

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጥቅምት 2/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ
በወርቅ ደረጃ ተሸላሚ የሆኑት 10 ድርጅቶች ሲሆኑ እነርሱም፡-

  • ሚድሮክ ወርቅ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • ሆራይዘን አዲስ ጎማ ኃ.የተ.የግ.ማ
  • አህፋ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • ኢትዮ አግሪ ሴፍት ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • የላይኛው አዋሽ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • ሚድሮክ ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • ዴይላይት አፕላይድ ቴክኖሎጂስ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • ኮንቦልቻ የብረታብረት ማምረቻ ኢንደስትሪ ኃ.የተ.የግ.ማ. (ኮስፒ)
  • ሆራይዘን ፕላንቴሽንስ ኃ.የተ.የግ.ማ ሲሆኑ
    በብር ደረጃ የተሸለሙት 8 ድርጅቶች ደግሞ፡-
  • ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • አዲስ ጋዝ እና ፕላስቲክ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • ዘመናዊ የህንፃ ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግ.ማ. (ኤም.ቢ.አይ)
  • ብሉናይል የፖሊፕሮፕሊንና ክራፍት ከረጢት ማምረቻ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • ሰሚት ኢንጂነርድ ፕላስቲክ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • አንሊሚትድ ፓኬጂንግ ኃ.የተ.የግ.ማ.
  • ሁዳ ሪል እስቴት ኃ.የተ.የግ.ማ. እና
  • ኩዊንስ ሱፐርማርኬቶች ኃ.የተ.የግ.ማህበር ናቸው፡፡
    ሽልማቱንም የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ እና የየድርጅቶቹ ዋና ሥራ አስኪያጆች ከክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እጅ ተቀብለዋል፡፡
    ሥራ አስኪያጆቹ ሽልማቱን በማግኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ በመግለፅ ለቀጣይ ዓመት ከዚህ ለተሻለ ዉጤት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
    እንደ ሃላፊዎቹ ገለፃ ይህ ዉጤት የተገኘው በሁሉም ድርጅቶች ስር ያሉ ሰራተኞች ጠንክረው በመስራታቸው ነው፡፡
    በቀጣይም ሰራተኞቹ በባለቤትነት ስሜት መስራት እንዳለባቸው ገልፀዋል።
    ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ2012 ዓ.ም መጨረሻ እንደ አዲስ ከመዋቀሩና የአመራር ለውጥ ከማድረጉ በፊት በስሩ የሚገኙ በርካታ ድርጅቶቹ ኪሳራ ውስጥ የነበሩና ለሠራተኞቻቸው ደሞዝ ለመክፈልም ጭምር ይቸገሩ እንደነበር ይታወቃል፡፡
    በ2014 ዓ.ም የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ሽልማት ላይ 12 የተቋማችን አባል ድርጅቶች በወርቅና በብር ደረጃ መሸለማቸው ይታወሳል።

Recent News

Archives

ABOUT MIDROC INVESTMENT GROUP

MIDROC Investment Group is a group of Sheikh Mohammed Hussien Ali Al-Amoudi’s companies, mainly engaged in Agriculture, agro-processing, Manufacturing, Mining, Construction, Real-estate, Hotel, Tourism and Commercial endeavors.

READ MORE

OUR LEADERSHIP

Our senior executives bring tremendous experience, visionary thinking and a shared commitment to excellence, creativity, and innovation to the future as well as  the day to day operation of the company.

READ MORE

  • AMANUFACTURING CLUSTER QUALITY POLICY